About AASTU Announcements Events News/Events

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዘርፈ-ብዙ ግልጋሎት የሚሰጡ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን አስመረቀ

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ጊዜያት የማህበረሰቡን ህይወት እና ኑሮ ሊያሻሽሉ የሚችሉ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡ ከነዚህም ውስጥ ከዚህ በፊት  ከሰራቸው አበይት ስራዎች መካከል ለ6 አቅመ ደካማ ወገኖች  የመኖሪያ ቤት እድሳት ፤ለአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች  መምህራን የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን መስጠት እንዲሁም በኮሮና ወረርሽን ወቅት አስፈላጊ የሆኑ ምግብነክ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ  ግብዓቶችን ለክፍለ ከተማው ማህበረሰብ እንዲዳረሱ አድርጓል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ የ90 ቀናት የልማት ፕሮጀክት ደግሞ ዩኒቨርሲቲው ለክፍለ ከተማው ማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ስራዎች ሰርቶ በዛሬው እለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ እና የክፍለ ከተማው ስራ አስፈፃሚዎች በተገኙበት ተመርቀዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በራሱ ወጪ አሰርቶ ለክፍለ ከተማው ያበረከታቸው ስራዎች ከዩኒቨርሲቲው የቱሉዲምቱ  በር እስከ ኮዬ ፈጨ አደባባይ ያሉ የመንገድ አካፋይ እና የመንገድ አደባባይ ማስዋብ፤ ለክ/ከተማው ማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ የዳቦ እና የአትክልት መሸጫ ሱቅ ፤እንዲሁም በክፍለ ከተማው የሚገኝ አንድ ቤተ-መፅሃፍት ከነ አጥሩ ሙሉ እድሳት በእለቱ ተመረቁ ስራዎች ናቸው፡፡

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ወቅት የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የፕሬዚደንቱ ተዋካይ የተቋማዊ ልማት እና ቢዝነስ ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተመስገን ወንድሙ ዩኒቨርሲቲው ለማህበረሰቡ የሰራቸውን ስራዎች ለእንግዶች አስጎብኝተዋል፡፡ ዶ/ር ተመስገን ዩኒቨርሲቲው በማህበረሰብ ውስጥ እንደመገኘቱ እና የህብረተሰቡን እድገት እና ለውጥ በብርቱ የሚፈልግ እንደመሆኑ የሚሰጠውን የማህበረሰብ አገልግሎት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡ ከመማር ማስተማር፤ የምርምር ስራዎችን ከመስራት በተጨማሪ የአንድን ማህበረሰብ ኑሮ ሊያሻሽሉ የሚችሉ የማህበረሰብ አገልግሎት ለህብረተሰቡ መስጠት ከዩኒቨርሲቲው ተልዕኮዎች ውስጥ አንዱና ዋንኛው እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

በቀጣይም ዩኒቨርሲቲው በጥናት ላይ የተደገፉ ማህበረሰብ ተኮር ስራዎች ላይ የራሱን አሻራ ለማሳረፍ እየሰራ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል፡፡

Related posts

በዩኒቨርሲቲው መምህራን እና ተማሪዎች የተሰሩ ስድስት የፈጠራ ስራዎች የአዕምራዊ ንብረት ባለቤትነት እና የቅጅና ተዛማጅ መብት የምስክር ወረቀት አገኙ

aastunew

Addis Ababa Science and Technology University and IIT ROORKEE Sign Partnership Agreement

aastunew

የ2013 በጀት ዓመት የስድስት ወር የበጀት አጠቃቀም መረጃ

aastunew

Leave a Comment

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy