About AASTU Applied Sciences Events News News/Events

ለሁሉም የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ድኅረ ምረቃ ትምህርት አመልካቾች በሙሉ

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ  ዩኒቨርሲቲ  በ2016 የትምህርት ዘመን በመደበኛ እና ተከታታይ መርሃ-ግብሮች መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን ከሐምሌ 19፤ 2015 ዓ.ም እስከ መስከረም 4 ፤ 2016 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው በይነ መረብ  በኩል ምዝገባ ማካሄዱ ይታወቃል፡፡

በዚህ መሠረት ለፈተና ያለፉ አመልካቾች ዝርዝር ከዩኒቨርሲቲው ድህረ ገጽ www.aastu.edu.et እና ኦፊሻል ቴልግራም https://t.me/pir2011  ማግኘት የምትችሉ ሲሆን አመልካቾች ከትምህርት ሚኒስቴር በተላለፈው መመሪያ መሠረት የሚከተሉትን ነጥቦች አውቃችሁ እንድተገብሩ አጥብቀን እናሳስባለን፡፡

  1. ሁሉም ተፈታኞች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው Graduate Admission Test (GAT) የመመዝገቢያ ፖርታል https://portal.aau.edu.et  ከመስከረም 21 25 2016 . ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ ማመልከት የሚገባቸው መሆኑን፣
  2. የመግቢያ ፈተና ከመስከረም 28 29 2016 . በሁሉም  የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በበይነ-መረብ የሚሰጥ መሆኑን፣
  3. ተፈታኞች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና (GAT) የመመዝገቢያ ፖርታል       ገብተው ሲያመለክቱ የመፈተኛ ጣቢያቸውን (ዩኒቨርሲቲ) እና ሌሎች መረጃዎችን በትክክል ተጠንቅቀው መሙላት የሚጠበቅባቸው መሆኑን፣
  4. ተፈታኞች በGAT የመመዝገቢያ ፖርታል ገብተው ሲሞሉና ሲያመለክቱ ፈተናውን  ለመውሰድ የሚያስፈልገውን ክፍያ ብር 1000.00/አንድ ሺህ ብር/ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ “Addis Ababa University Main Campus” በቴሌ ብር አካውንት 511001 በኩል ብቻ የሚከፍሉ በመሆኑ ከወዲሁ የቴሌ ብር አካውንት መክፈት እና  ዝግጁ ማድረግ የሚጠበቅባቸው መሆኑን፣
  5. ተፈታኞች የፈተና ፕሮግራሞችና ተያያዥ መረጃዎችን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ድኅረ- ገጽና ፖርታል www.aau.edu.et  እና https://portal.aau.edu.et እንዲሁም ኦፊሻል የቴሌግራም ቻናል ማግኘት የምችሉ መሆኑን፣
  6. በየትኛውም የመፈተኛ ማዕከላት ለፈተና ለመቀመጥና ፈተናውን ለመውሰድ ተፈታኞች  ፎቷችሁ ያለበትን Test Admission Ticket (TAT) ከ (http://portal.aau.edu.et/web/applyForAdmission/TestTaker)  አውርደው እና ፕሪንት አድርገው መያዝ የሚጠበቅባቸው መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ 

       የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ  ሬጅስትራርና አሉምናይ ዳይሬክቶሬት

Related posts

Prof. Bankart Charles from University of Kansas has visited AASTU.

Mr. Abebe Dutoro

aastunew

To All Interested Researchers

aastunew

Leave a Comment

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy